Total Pageviews

Saturday, March 30, 2013

ቁጭ በል-ካ በመሬት

    ጊዜው ትንሽ ረዘም ብሏል የደርግ ጊዜ በመባል የሚታወቀው ወቅት ነው፡፡ ሁኔታው የተፈጠረው ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ድሬዳዋ በሚሄድ ባቡር ላይ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ከአዲስ አበባ ድሬዳዋ ጅቡቲ መንገደኛ ይዞ የሚጓዝ ባቡር ነበር፡፡ ከዚህ ቀደም ሲልም የማታው ባቡር መኘታም ነበረው፡፡ ለማንኛውም መነሻቸውን ከአዲስ አበባ ያደረጉ ተሳፋሪዎች በዋዜማው በአዲስ አበባው ላጋር ባቡር ጣቢያ ቲኬታቸውን ረጅም ሠልፍ ተሰልፈው ቆርጠው በመሄጃቸው ቀን ሌሊት በ11 ሰዓት ሄደው ተሣፍረው ናዝሬት ደረሱ፡፡  የትዕዩንቱ ባለታሪኮች አንዲት ሴትና ሕፃን ልጇ፣ አንድ ወጣት፣ ሌሎች ተሣፋሪዎች፣ እንዲሁም ፈንጠር ብለው የተቀመጡ የአደሬ አዛውንት ናቸው፡፡ ወጣቱና እመጫቷ አንድ ወንበር የተጋሩ ቢሆንም ወጣቱ ለእመጫቷ ከነልጇ እንዲመቻት ወንበሩን ለቆ በፉርጐው በራፍ ላይ ቆሟል፡፡ ባቡሩ ናዝሬት ላይ ሲቆም አንድ ተሣፋሪ በዚህኛው ፉርጐ ይገባል፡፡ ዙሪያ ገባውን ይመለከታል፡፡ ትርፍ ወንበር ያጣል፡፡ ትርፍ ነው ብሎ የገመተውን ቦታ እናቲቱና ልጅ የያዙትን

                  “ልጅሽን እቀፊና እኔ ወንበሩ ላይ ልቀመጥ” ይላል፡፡
    በዚህ ጊዜ ቦታውን የለቀቀው ወጣት ፈጠን ብሎ ጠጋ ይልና “እኔ እንዲመቻት ብዬ ነው የለቀቀሁላት እንጂ ለመቀመጥማ ቦታው የኔ ነው ይላል፡፡ አንድ ሁለት ሲባባሉ ጠቡ የሁሉም የባቡር ተሣፋሪ ጉዳይ ይሆናል፡፡ ተሣፋሪው ግለሰብ በየዘመኑ በአገራችን ብቅ የሚሉና “የዘመኑ ሰው” በመባል የሚታወቁ ልበ ሙሉዎች አንዱ መሆኑን በጐኑ የታጠቀው መሣሪያ ኮቱን ገለጥ አድርጐ በማሳየት በሕብረተሰቡ ውስጥ ያለውን ቦታ በቃል ብቻ ሳይሆን በድርጊት ያሳያል፡፡ አብዛኛው ገላጋይ ድምፁን እየቀነሠ ይሄዳል፡፡ ፍጥጫው ባለወንበሩ ወጣት፣ የሕፃኑ እናትና በባለ ሽጉጡ ልበ ሙሉ መካከል ይጦፋል፡፡ እስካሁን ቃላቻውን ያልሰጡት በመስኮት ወሬ እያዩ ጥርሳቸውን የሚፍቁት አዛውንት “የኔ ወንድም” ብለው ጉሮሮአቸውን አጥርተው በጉዳዩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጣልቃ ይገባሉ፡፡

                        “እስቲ ና ወዲህም” ይላሉ፡፡

    ጐበዙ የባቡር ላይ ጀግናም ምናልባት ፍትህ ከእሳቸው አገኝ ብሎ ፊቱን ወደ አዛውንቱ ያዞራል፡፡ እሳቸውም የአደርኛ ለዛ በብርቱ በተጫነው አማርኛ (ተሰልፈው ቲኬቱን ሲገዙ ጀምሮ ጠዋት ሲሳፈሩ የነበረውን ድካምና እንግልት በዝርዝር ያስረዱታል፡፡ አንተ አሉት “እኛ ሌሊት 10 ሠዓት ላይ ተነስተን ወረፋ ይዘን ስንሳፈር ተኝተሃል፡፡” “አሥራ አንድ ሰዓት ላይ ባቡር ላይ ስንወጣም ተኝተሃል፡፡ እንቅልፍህን ጠግበሃል፡፡ ቁርስ በልተሃል፡፡ ሻሂ ጠጥተሃል፡፡ ሲጋራህን አፍህ ላይ አድርገሃል፡፡ እና፡፡ ይላሉ የአደሬው አዛውንት (ወደ ፍርድ ውሳኔያቸው አንደርድሬ ልውሰዳችሁና)  “የኔ ወንድም! ቁጭ በልካ በመሬት!” አሉና ፊታቸውን ወደ ባቡሩ መስኮት አቃንተው እየተመለከቱ ጥርሣቸውን መፋቅ ቀጠሉ እኛ የተጓደለብን ምቾት ስላገኘህና ትርፍ ወንበርም ባለመኖሩ ወንበር ከሌለ የሚገባህ፣ መሬቱ ነውና መሬት ላይ ቁጭ በል ማለታቸው ነው፡፡ የፍርጐው ሰው ሁሉ ይስቃል፡፡ መንግሥቱ ለማ “ብራቮ” ተባለ ነው ያሉት? በባሻ አሸብር ላይ? እንደዛ ተባለ፡፡ ሰውየው ኩምሽሽ ይላል፡፡ እመጫት ከነልጇ ተስፋፍታ ትቀመጣለች ፍርጐው ውስጥ ሠላም ይሠፍናል፡፡ የዚህ ዳኝነት ባለቤት እኒያ “ቁጭ በል ካ በመሬት” ያሉ አዛውንት ናቸው፡፡

ተንደርድረን ወደዚህ ዘመን እንምጣ፡፡ የተፈጥሮ ሕግ ነውና በየቀኑ በተለያዩ የኑሮአችን ግንኙነቶች እንዲህ ያሉ ዘመናይ የሰው መብት ተጋፊ ጉልቤ ማን አለብኝ ባዮች ያጋጥሙናል፡፡ በቅርቡ በአንድ ጋዜጣ ታክሲ ላይ ሽጉጣቸውን በገንዘብ አስከፋዩ ላይ ያወጡ ሰው ተከሰሱ የሚል ዜና ተመልክቻለሁ፣ በየቡና ቤቱ ይሄኛው  ዘፈን ለምን ተዘፈነ ብለው ቡራከረዩ የሚሉ፣ በጐናቸው የታጠቁትን ሽጉጥ እያሳዩ የሚገሠሉ፣ በየመንገዱ የወጣት ሴቶችን ስለማዊ ጉዞ የሚያውኩ፣ ጊዜ በሠጣቸው ሥልጣን የሰው አጥር የሚገፉ ማን ይናገረኛል ባይ ጡንቸኞች፣ ያጋጥሙናል፡፡ እናስ እንደ እኒያ አዛውንት “ቁጭ በል ካ በመሬት” የሚል ብዙ ሰው አለ?

አለፍ ከፍ እንበል ባለሥልጣን ሲሳሳት፣ የሥልጣን ብልግና ሲፈፀም፣ ባለ ገንዘብ ከሕግ ውጪ ሲሆን፣ ጐረምሶች መሬቱ ጠበበን ሲሉ እስቲ ቆይ እዚች ላይ አቁሙ የሚሉ ብዙ ሰዎች አሉ?
አለም የለምም የምትሉኝ ጻፉልኝ!




   ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የቆዩ የሬዲዮ ጋዜጠኛ ናቸው፡፡ ላለፉት አስራ ምናምን አመታት በየጨዋታ እንግዳ የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ለጋዜጠኛ መዓዛ የምንለው አለን የምትሉ meaza.birru@shegerfm.com ይጻፉ፡፡ ወይንም በዚሁ ብሎግ ላይ አስተያየታችሁን ማስፈር ትችላላችሁ!

28 comments:

  1. we have to stop such kind of people now.Other wise things has gona be move in the wrong direction,All the morals and values that we respected will not be maintained by all groups.

    Nice View Meaze

    ReplyDelete
  2. Well the Woman is Highly Experienced and good enough for the local Audience. but The station she rocks is I think getting out of the business. they're nat doing like they used to some 3 or 2 years ago. That is Because 1, The station's Programs lack substance rather simple amarigna Style which has already bored the city.
    2, Apart from the depth Problem , the station's stance is nat clear in
    national issues which sometimes Makes it "ETV in Radio"
    3 , They're stuck in A complacency. they should Get Creative ,
    They Should Get out of their Aged Mentality as the Woman
    and her company are in their late 50s. This generation needs
    New Fresh Creative And Appealing radio station that
    Enhances their life and Adds something to their days.
    IF a new FM station Emerges , Sheger Will fall soon

    ReplyDelete
    Replies
    1. Well... the issue is not about the fall of the station it was about how to stand the bullies, I think it's your wish to see the fall of Sheger FM. May be if you spent less time on capitalizing your words and more time on reading the blog, you will for sure contribute something to the community.

      Delete
    2. Bravo Abyneh! You told that guy who named himself after temple of Merry the right answer.

      Delete
  3. This comment has been removed by the author.

    ReplyDelete
  4. This comment has been removed by the author.

    ReplyDelete
  5. Thank you meaza for bringing this issue for the public attention. I have also heard same issue on your Abdu's table what is new session last day regarding the person who take out a pistol aboard on taxi. I do personally encountered few individuals who wants to boost at balcony of the bars and groceries in Addis Ababa showing their pistol and taking out loud as if they are "General" in command of that community .in addition they think themselves as they are the protector of the community with out any representation simply due to either their affiliation to the government or due to their stupidity. They did not consider the people of Addis Ababa is very closely so they should be told by the concerned ones or the issue should be addressed in public media for discussion. Thank you

    ReplyDelete
  6. Draw lesson from past

    Noble issue. Yes, Maza ,as she always does, has amazing stories to tell. This one-though too short compared to my expectation- weighs much. Individuals whom time favours them think that their legacy would remain for eternity. But, 'time' surely makes everything up-side-down and such individual's fate will be facing shame, failure.... we need to take lesson and seat 'on the ground'- ka Meret- even if we are enjoying public power. For two things. Firstly, the power will vanish like 'a fog.' Secondly, it is the people who conferred the power upon us ("Us?" I have no power. Neither favoured by the time.) and the people need respect. Every 'Gura kereyou' is at the expense of the people. So lets draw lesson from the past! Thanks Maza!!

    ReplyDelete
  7. meaza betem betem new yemiwedish egziabhiher edimena tena yistish.

    ReplyDelete
  8. Gobez malet min malet new? Bilo lemiteyik sew mels yehonish gobez sew::

    ReplyDelete
    Replies
    1. Lek bilehal wondeme. Ene mechem endesua Leza yalew sew ayechem alaweke! Enchete enchete emilewen neger hulu eko new nefse emitzerabet!

      Delete
  9. Hello Eteye meaza በጣም ጥሩ ፅሁፍ ነው አስታውሳለሁ የዛሪ 15 አመት በፊት ፓሰተር አካባቢ አንድ የታክሲ ረዳት ተግድሎአል

    ReplyDelete
  10. Dear Meaza,

    i am sure there are a lot of people like the one who said "bura kereyo" but i doubt there is almost no one who is like the elderly man who said "kuch bel ka meret". because now a days people are thinking that they have no right in any thing they just have to go with flow i think ... may be they will try to attack the elderly..lol

    ReplyDelete
  11. Etiye Mazi, first and most i would like to appreciate the whole thing what you are contributing to your people and country.
    journalism is not easy task it needs its own techniques, approach, facing challenge, paying attention, handling people interest, teaching the community ..... There are so many things i can mention in this regards. And also to fulfill these above requirements it needs a commitment and adequate knowledge.
    Meazi is among little Ethiopia journalist who is qualified these requirement. That is why I’m always be eager to lesson and read her media production for the last ten and above years. i have been heard more than hundreds interview with legend Excellency Ethiopians.
    for sure these in interview by itself would be a big historical museum .
    that is what i want to say about Etiye meazi .
    let's back to today's topic I can agree with her 100% what she mentioned on her story .this is what we always pull us to back ward when somebody makes wrong we are not ready to face him ,to give him correction or ask him "why" we always keeping silent until a problems come and enter to our home .
    so in this regard we need to be change we have to stand for those who are victim of dictator .

    ReplyDelete
  12. Please shgeroch don't use this little funny boxes cos I don't understand what it means and also there will be manny more people who don't understand either so please use proper Amharic fidel thanks.

    ReplyDelete
  13. Here is another story on the topic but a bit different and funny. It happened in Jigjiga.
    Three young men (friends) were hanging out jumping from bar to bar. They got drunk and were so happy durin that night. While getting into one of the bar, they came across a guy with two girls (a type of guy who love to be sandwiched by girls ). As young folks, they began to dance arround them. You know what I mean: they were wooing those girls. The guy became angry and started fighting (just in words) with those young men. Before long, two of the young men stopt arguing and they try stop their friend (the youngest of all) but he insisted and continued replying. The guy told the young man to follow him out of the bar to talk alone. The young man did so. When the young man catch up with the guy, the man huged the boy and then he put the pistol right on the young man's stomach. Then he said, "would you mind leaving this bar?". When the young threw his eyes down towards his stomach, he noticed that thing was real pistol. The he replied, "sure! I'll"... "dibin adrge ehedalehu!"... The point here is that there are lots people who pullout guns here and there with silly reasons. They use guns to accomplish personal interests though they armed to keep public security.

    ReplyDelete
  14. መአዝዬ በጣም እንወድሻለን፡፡ እንግሊዝኛው አይገልጽልኝም ብዬ ስላሰብኩ ነው በአማርኛ የምጽፍልሽ፡፡ ሁሉም ነገርሽ ኢትዬጽያዊ፤ ህዝባዊ በተላይም ዛሬ ለሆዳቸው ያደሩ ጋዜጠኞች ሃገራችንን በሞሉበት ወቅት አንችንና ሸገርን ስላገኘን ምን ያህል ደስተኞች እንደሆንን መግለጽ አልችልም፡፡
    በቃ እንግዶች ሽን እኝ መጠየቅ የምናስበውን ትጠይቂልናለሽ፤ ቁጭት፤መንፈሳዊ ቅናት፤ሃገራዊ ወኔሽ ግሩም ነው
    ሁሌም ኑሪልን፡፡ አደራሽን በሌላ ጣቢያ እንዳትኄጅብን በተለይ አረ ሌም የለ ከሸገር ውጭ ሁሉም ያው ናቸው
    እግዚአብሄር እድሜሽን ያርዝምልን
    መአዝዬ በጣም እንወድሻለን፡፡ እንግሊዝኛው አይገልጽልኝም ብዬ ስላሰብኩ ነው በአማርኛ የምጽፍልሽ፡፡ ሁሉም ነገርሽ ኢትዬጽያዊ፤ ህዝባዊ በተላይም ዛሬ ለሆዳቸው ያደሩ ጋዜጠኞች ሃገራችንን በሞሉበት ወቅት አንችንና ሸገርን ስላገኘን ምን ያህል ደስተኞች እንደሆንን መግለጽ አልችልም፡፡
    በቃ እንግዶች ሽን እኝ መጠየቅ የምናስበውን ትጠይቂልናለሽ፤ ቁጭት፤መንፈሳዊ ቅናት፤ሃገራዊ ወኔሽ ግሩም ነው
    ሁሌም ኑሪልን፡፡ አደራሽን በሌላ ጣቢያ እንዳትኄጅብን በተለይ አረ ሌም የለ ከሸገር ውጭ ሁሉም ያው ናቸው
    እግዚአብሄር እድሜሽን ያርዝምልን

    ReplyDelete
    Replies
    1. Eneme endezaw ante degmo yelben selsafkelgng Egzare yestelgne.
      Me and my family loves Meaza a lot may God give you long life.

      Delete
  15. Dear Meaza, no words about you at all... just more than phenomenal!!! and to your FM radio station amazing qualified journalists and seducing programs as well.Keep it up!!!...And about the above blog,... just let us protest and end such low level thinkings afterwards and stand together to draw the best and better... BLESS...

    ReplyDelete
  16. I have been a big devotee for years. Starting from the time you were presenting Chewata @ FM 97.1. I certainly can tell that there is no journalist in this country that is so brilliant, all rounded, respect persons from the heart & doing it all in an Ethiopian manner. Rejim Edme yistelen. Leseteshin bemulu enamesegnalen.

    ReplyDelete
  17. nice view meaza please we want more ideas that inspire our demoralized generation

    ReplyDelete
  18. በጣም ጥሩ ርዕስ አካፍለሽናል እናመሰግናለን፡፡ በየጊዜው በተለያየ መልኩ የሚገጥመን ጉዳይ መሆኑንም መግለፅ እፈልጋልሁ፡፡ በአስተሳሰባቸው ሳይሆን በያዙት መሳሪያና ስልጣን የሚተማመኑ ሰዎች በእንዲህ ዓይነት አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን በብዙ መልኩ የሰውን ህይወት የሚበጠብጡ ብዙ ናቸው፡፡ ነገር ግን እንዲህ አይነት ሰዎችን በዘመናዊነት መግለፅሽ አላሳመነኝም፡፡ ዘመናዊነት ምንም የቃላት ወይም የትርጉም ችግር የለበትም፡፡ የሰውልጅ በሙሉ የየራሱ ዘመን አለው፡፡ ሁላችንም ለዘመናችን ዋና ተዋናይ ሆነን ማለፍ እንዳለብን አምናለሁ፡፡ በዛ ዘመንም መጥፎም ሆነ ጥሩ ነገሮችን ከዚህ በፊት ከምናውቀው በተለየ መልኩ ልናስተውል እንችላለን፡፡ ጥሩውን በመቀበል እና በማሳደግ መቀጠል ሲኖርብን መጥፎውን ደግሞ መጥላት እና ጥሎም መሄድ ይኖርብናል፡፡ መኮነንም ያለብን ድርጊቱን እና ስህተቱን እንጂ የሆነበትን ጊዜ አይመስለኝም፡፡ አመሰግናለሁ!

    ReplyDelete
  19. ከየት መቶ መአዚ፡፡ እንደውም የሃገራችን ትልቁ ችግር አንዱ አንዱን ከመገሰጽ ይልቅ አንዱ ላይ ግፍ ሲፈጸም እኔ ላይ ካልደረሰ ምን አገባኝ የሚሉት ነገር ነው

    ReplyDelete
  20. beminorbet sefer yayewutn lingerachu. yeminorewu ezihu addis abeba gofa mebrathayl newu. liju yserkna ejkefnj yiyazal sbseb bilewu ezawu kemigegnewu mebrart hayl gibi kalu wotaderoch ywosdutal. ketaksi wrja salf godegnochan agegnwuna komku(Ethiopiawi wora ayto malf aychlm) negeru btam asgermogn mayeten ketlku. yhahulu sewu baynu aytot ejkefinj tyzo liju belaba ayne derknet afito kade kezam ejulay yregewun seat eyaye endt bilo afefetetebachewu wotaderochum gira bemegabat smit beka wanawu ekawu alemetfatu newu bilewu sewun betnut lijunm lekekut. liju(lebawu) yaregewu seat yeand parti milkt arma yeneberwu newu:: negeru betam germogn wodebet hedku::

    ReplyDelete
  21. ከጥቂት አመታት በፊት የጋዜጠኝነት ትምህርቴን ወደምከታተልበትና አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት አጠገብ ወደሚገኘው ግቢ አመራለሁ፡፡መነሻዬ ከጦር ሀይሎች ነበርና ከጦር ሀይሎች ፒያሳ በሚለው የተሳፈርኩበት ታክሲ ብዙ ወጪ ወራጆች ቢኖሩም እኔ ግን ከመነሻ እስከ መድረሻ ተጓዥ ነበርኩ፡፡
    ከወጪ ወራጆቹ መሃል የሆነ ቦታ ላይ እድሜያቸው በሰላሳዎቹ የሚገመት ሶስት ወንዶች ወደ ታክሲው ገቡ፡፡ሁለቱ ከታክሲው የኋላ ወንበር ሲቀመጡ አንዱ ከእኔ ጎን ክፍት ከነበረው ወንበር ተቀመጦ ጉዞ ቀጠልን፡፡ ፊቴን ወደ መስታወቱ አዙሬ የውጩን ትዕይንት እየተመለከትኩ ቢሆንም አጠገቤ ያለው ሰው ትኩረቱ ወደኔ እንደሆነ ስሜቴ ይነግረኝ ነበር፡፡ያም ሆኖ ከንግግር ይልቅ ዝምን የፈለኩበት ሰዓት ነበርና የሰውየው ሁኔታ ምቾት ቢነሳኝም ምንም ያላወቅኩና ከታክሲው መስታዎት ባሻገር ባሉት ትዕይንቶች የተመሰጥኩ መስዬ መጓዜን ቀጠልኩ፡፡
    ንግግር ጀመረ፡፡ከእሱ ጋር ንግግር ለመጀመር ፍቃደኛ አለመሆኔን ቢረዳ በሚል አንድ ሁለት ንግግሮቹን መልስ ባለመስጠት አሳለፍኩ፡፡የሚናገው አማርኛ የትግርኛ ተናጋሪነቱን አጉልቶ የሚያሳብቅበት የታክሲ ውስጥ ወንበር ተጋሪዬ እንዲህ በቀላሉ የሰው ስሜት የሚረዳ አለሆነ ኖሮ መንዘባዘቡን ቀጠለ፡፡ እኔ ደግሞ ለወሬ ፍላጎት አልባ ከመሆኔም በላይ የሰውዬው ድርቅና እና የማይስበው አወራርና ርዕሰ ጉዳዩ የብስጭት ደወሌን ሊነቀንቃት በመከጀሉ ከረር፣ኮስተር ያሉ ቃላትን እናገር ጀምሬያለሁ፡፡
    ስሜን ጠየቀኝ ፤ልነግረው እንደማልፈልግ ነገርኩት፡፡ ምክንያቴን ሲጠይቀኝም አለመፈለግ እንደሆነም አከልኩለት፡፡ ሰውዬው አይቶ ብቻ ሳይሆን ተነግሮትም ሰውን የሚረዳ እንዳልሆነ ያረጋገጥኩት ከዚህ በኋላም ጭቅጨቃውን ባለማቆሙ ነበር፡፡ እጅግ የገረመኝና ዛሬም ድረስ የሚደንቀኝ ነገር የሆነው ግን ቀጥሎ ነው፡፡
    “ይቆጭሻል!” የሚለውን የሰውየው ቃል ስሰማ የነሳሁትን ፊቴን መለስ አድርጌ በግርምት አየሁት፤አለባበሱም ሆነ ሁኔታው ከሌላው ሰው የተለየ አይደለም፡፡ይሄን እያጤንኩ ጥያቄዬን ሰነዘርኩ፡፡ “ምኑ ነው የሚቆጨኝ አንተን አለመተዋወቄ?”
    እፍረት ያልፈጠረበት የታክሲ ውስጥ ወንበር ተጋሪዬ መለሰልኝ “አዎ”
    “ምን ስለሆንክ?” ንዴቴ በአንድ ሁለት ደረጃ ከፍ ቢልም ቅላፄዬ ውስጥ ከንዴቴ ይልቅ ንቀቴ እንደተንፀባረቀ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡
    ቶሎ አልመለሰልኝም፡፡ መልሱ ሲቆይብኝ ዞር ብዬ አየሁት ሰረቅ ሰረቅ አድርጎ የሰዎች አይን እንዳረፈበትና እንዳላረፈበት ቃኝቶ መለስ ሲል ተገጣጠምን፡፡ ወዲያው በኔ በኩል የነበረ የጃኬቱን ግራ ጎን ገለጥ አድርጎ ከጎኑ የተሻጠ ነገር አሳየኝ፡፡ ሽጉጥ፡፡ አልደነገጥኩም፡፡
    “ምን ማለት ነው?” ከንዴቴ ይልቅ በእጥፍ የጨመረው ንቀቴ እንዳወጣ የፈቀደልኝ ቃል ይሄ ብቻ ነበር፡፡ “ምን ማለት ነው?”
    “በሰላም ወጥተሽ የምትገቢው በእኛ ነው፡፡”
    “እናንተ እነማን ናችሁ?”
    መልሱን በጣም ብፈልገውም አልመለሰልኝም፡፡ እነ እገሌ ነን ብሎ እንደማይመልስልኝ ሲገባኝ አቅጣጫዬን ከማንነቱ ወደ አይረቤ ድርጊቱ መለስኩና “ይሄኮ የሰላም አስከባሪነትህ ማረጋገጫ ሊሆን አይችልም፡፡” አልኩት፡፡
    “እንዴት አይችልም?” ጠየቀኝ፡፡
    “ሰላም አደፍራሾችም ይህን ይይዙታል፡፡ ከእነሱ አንዱ ላለመሆንህ ምን ማረጋገጫ አለህ?” በተራዬ ጠየቅኩ፡፡
    ለጥያቄዬ መልስ አልሰጠኝም፡፡አብረውት የገቡትና ከኋላ ወንበር የነበሩት ሰዎች ታክሲውን አስቁመው መውረድ በመጀመራቸው ተከትሏቸው ወረደ፡፡ቆይታው ረዝሞ መጨረሻውን ባይ ምኞቴ ነበረ፡፡ ያ ሳይሆን ቀርቶ ነገሩ በእንጥልጥል እንዳለ ቢወርድም ለእኔ ግን ዛሬም ድረስ ሳስታውሰው የምገረምበትና እንዲህ አጋጣሚው ሲፈቅድ የማወጋው ትቶልኝ ሄዷል፡፡ ዛሬም የመዓዛን “ቁጭ በል ካ በመሬት” ሳነብ ትውስ ያለኝ ይህ ገጠመኜ ነው፡፡ የኔውኑም ሰው “ቁጭ በል ካ አርፈህ” እንበለው ይሆን?
    እየሩሳሌም ዳኜ

    ReplyDelete
    Replies
    1. እየሩስ በጣም የሚገርም ነገር ነው ፡፡ አሳፈረሽኝ አንቺና ሌሎች ጭፍን ሰዎች እነደምትሉት ዘመኑ የትግራይ ሰዎች ናቸው ይህን የሚያደርጉት ብለሽ ነው ለአስተያየትሽ ማጣፈጫ ያደርግሽን ፡፡ ያሳፍራል እኔ ይህንን እንኳን የትግራይ ሰው አይደለም ከዚህ በላይ የሚያደርጉ ሰዎች እያሉ ዘለሽ ትግራይ ላይ ምን አፈናጠጠሸ ፡፡ ጠባብ ነሽ ፡፤ የተከበሩት አንቺ ልበላት በጣም ስለምወዳትና ስለ ማከብራት የተከበረችው ወ/ሮ መዓዛ ያነሳችው አርእስት ከግብረገብነትና አጉል ትእቢት የተነሳ የሚደረጉ ድርጊቶች ነው ፡፡ አንቺ ግና የትግራይ ልጆች ሽጉጥ ይይዛሉና ሽጉጡ ጋር ነው ጉዳይሽ ፡፡ ደግሞም ሌላው ችግርሽ ሊለክፍሽ እንደሞከረና ፊት እንደነሳሽው እንጂ አንቺ ተነሽ ኋላ ይቆጭሻል አላለም ፡፡ ስለዚህ እነ እየሩስ እባካችሁ ተውን መጋጨት የምትፈልጊው ግንብ ጋር መጋጨት የአባት ነው የትግራይን ሰው ግን ለቀቅ ….

      Delete
  22. what i understand from the story is the power of the old woman at that time and even he didnt respond a word about it,Meaze today's is different,they don't give a sheet for any thing they'r blind ,trying to show their power,..and they are supported by members of the group(police,security officers and,...) so today is different,as you mention last time they even accept elders but today,...today,.. meaze yeteshalew laymeta kentu mignote honobegnal lene,...we are loosing the social factor!!!!! even the govt dont want to say any thing about it,... very hard!!!!!!

    ReplyDelete