Total Pageviews

Saturday, April 27, 2013

“Don’t Judge a book by its cover “አሉ ፈረንጆቹ ሙድ ሲይዙብን



“Don’t Judge a book by its cover “አሉ ፈረንጆቹ ሙድ ሲይዙብን
ፍተሻ አለም ላይ
ፍተሻ ለግል ፤ለማህበረሰብ እና ለሀገር ደህንነት ያለው አስተዋፅዎ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ሁላችንም የምንስማማበት ይመስለኛል፡፡ከደህንነት ጥበቃ ማነስ አንጻርም የስንቱ ህይወት በከንቱ እንደቀረም የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ለዚህም ነው ሀገሮች ከምንም በላይ ለጥበቃቸው ትኩረት ሰጥተውና ዳጎስ ያለ በጀት መድበው የሚንቀሳቀሱት፡፡
ፍተሻ እኛ ሀገር
ስለፍተሻ ጉዳይ ሳስብ በአየር መንገድና በከተማችን በሚገኙ ትላልቅ ሆቴሎች ያለው አስተማማኝ የጥበቃና የፍተሻ ሁኔታ በጣም ያረካኛል፡፡ሁሉም ለራሱ ደህንነት ሲል እኩል የሚፈተሽበት፡፡ ያውም በደስታ በነጻነት፤ ያለፍርሀትና የደህንነት ስጋት ሳያጋጥመን ለመዝናናት፤ለመስራት ብሎም ለመጓጓዝ፡፡ነገር ግን……….ነገር ግን ዐረፍት ነገሩን አፍራሽ ያደርገዋል ተብለን አይደል የተማርነው ፡፡
እና እኔም ነገር ግን ብያለሁነገር ግን በፍተሻ ቦታዎች ላይ( በአንዳንድ ሆቴሎች፤ባንኮች ፤የመዝናኛ ስፍራዎች፤ሲኒማ ቤቶችወዘተ) እየደረሰብን ያለው መገለልና መድሎ ይቁምልን ነው፡፡እንዴ ሰው ባገሩ እንዴት ..እንዲህ አይነት መድሎ ይደርስበታል፡፡ቆይ እኔ ምለው ለሀገር ደህንነት ስጋት መሆን ያለበት ኢትዮጵዊ ነው ወይስ የውጪ ዜጋ(እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው ሁሉም የውጪ ዜጋ የሀገር ስጋት ነው፤ኢትዮጵያዊ ደግሞ የሀገር ስጋት ሊሆን አይችልም የሚል የጅምላ ድምዳሜ ላይ አልደረስኩም)፡፡ ነገር ግን ቀለሙ ነጭ ስለሆነ ብቻ ከስጋትና ከጥርጣሬ ነጻ መሆን አለበት ወይ? እንደኛ ቀለሙ ስለጠቆረ ደግሞ(ያውም በገዛ ሀገሩ) መጠርጠር አለበት ወይ ነው ጥያቄዬ? “ባለቤቱ የናቀውን አሞሌ ባለእዳ አይቀበለውምአይደል ተረቱ:: ቆይ እርስ በእርስ ከተጠራጠርን ማን ሊያምነን ነው??? ከሀገሬ ወጣ ስል ለሚያጋጥመኝ የተንዛዛ ፍተሻ አሪፍ መጽናኛ አለችኝ እንዴ የኔው የራሴ ሰዎች እንደዚያ አገላብጠው ከፈተሹኝ ባዕዶቹማ እንዴት አይበረብሩኝ? ብዬ እፅናናለሁ፡፡
ከሁሉም ግን ግርም የሚለው ነገር፡፡በገዛ ሀገራችን አንድ አይነት ቦታ ላይ ነጮቹ ሳይፈተሹ ሲገቡ እኛ አንዳንዴ ስብዕናችንን በሚፈታተን መልኩ የምንበረበረው ነገር ነው፡፡አንዳንዴ ንዴታችሁ ብልጭ ብሎባችሁ ለምን የውጪ ዜጎቹ እንደማይፈተሹ ጥያቄ ካነሳችሁማ በቃ ጭራሽ አትገቡም ልትባሉ ሁሉ ትችላላችሁ፡፡
አንዴ እንዲህ ሆነ…
አንድ ስብሰባ ነገር ነበረችኝ፡፡ቦታው በከተማችን ካሉት ትላልቅ ሆቴሎች በአንዱ ነው፡፡ የኔ ስራ ለውይይቱ መነሻ ሀሳብ የምትሆን ጽሁፍ ቢጤ ማቅረብ ነበር፡፡በወቅቱ ቀጫጫ ቤጤ ነበርኩና ያው እንደሚታወቀው እኛ ሀገር ለመከበርና አንቱታን ለማግኘት ስጋ፤ ቦርጭና አለባበስ ግድ ይላል፡፡ያኔ ጥሩ ለብሻለሁ ስጋና ቦርጭ ግን አልነበረኝም ፡፡ማህበረሰባችን ደግሞ እንደ ፋሲካ በግ ከላይ አይቶ ነው የሚገምትህ ምክንያቱም “Don’t Judge a book by its cover “ የምትለውን አባባል አያርፍማ፡፡
እናም ትንሽ አርፍጄ ነበርና በር ላይ ስቻኮል ለፍተሻ ሁለት የሆቴሉ ጠባቂዎች መኪናችንን ያስቆሙናል፡፡እሺ ብለን አቆምንና መኪናችንን አገላብጠው በረበሯት፡፡ሞተር መፍታት ነው የቀራቸው፡፡ጋራዥ ነው እንዴ እስክንል ድረስ፡፡ይሄም አልከፋንም በጄ ብለን ነበር፡፡እኔም ሾፌሩም ውረዱ ተባልን፡፡ወረድን፡፡እኛንም ልክ እንደመኪናዋ በረበሩን፡፡ ኧረ ሞተር እንዳይፈቱብን ተባብለን ተሳሳቅንም ተሳቀቅንም፡፡
ወዴት ነውየሴቷ ጥበቃ ጥያቄ ነበር
ይቅርታ የኔ እህት ሆቴል መስሎኝወዴት ነው ተብሎ ይጠየቃል እንዴ ..? ትንሽ ጥያቄው አናዶኝ ነበር
ማነሽወዴት እንደሆነ ካልተናገርሽ አትገቢም” …በቁጣና በገልምጫ
ሾፌሩ ትንሽ እንደመናደድ እየቃጣው ስለኔ መናገር ጀመረ
አይመለከትህም እሷ ትናገር…”
ስነ ስርአት….” አለ በንዴት ሾፌሩ
በዚህ መሀል አምስትና ከዛ በላይ የሚሆኑ ፈረንጆችን የጫነች ሚኒ ባስ ያለ ክልከላና ያለ ጠያቂ ሰተት ብላ ገባች….አይኔን ማመን ነው ያቃተኝ፡፡ማንም የተናገራት የለም፡፡ በዚህ ቢበቃ እኮ ጥሩ ነው፡፡ ጀርባቸው ላይ አነስ ያለች መኪና የምትጭነውን ያህል ትልቅ ቦርሳ፤ የስፖርት እንዲሁም የሙዚቃ መሳሪያዎችን ያየዘ ሌላ ቦርሳ የተሸከሙና ተራራ ወጪ የሚመስሉ ሶስት ፈረንጆች ቀጥ ብለው ገቡ፡፡ወዴት ነው? እንዴት ነው?ማናችሁ? ያላቸው ሰው አልነበረም፡፡
ይሄኔ ሾፌሩ መሳደብ ጀመረእኔ በቃ የምናገረው ነገር ግራ ገብቶኝ ቆሜያለሁ፡፡በዚህ መሀል ወንዱ ጥበቃ መጣና ከኛ ጋር ክርክር ጀመረ፡፡
የኔ እመቤት የስብሰባው ሰዓት እረፍዶብኛል እባክሽ በኋላ እንነጋገራለን ..አሁን ልግባበጣም በትግስትና በአክብሮት ነበር የጠየኳት፡፡አሻፈረኝ አለች፡፡
እንድዉም መኪናውን አውጣ ምናምን መባል ተጀመረአሁን እኔም ተናደድኩ……ስብዕናዬን ተፈታተኑኝ፡፡ወንዱ ጥበቃ በመሀል መታወቂያ አለ፡፡
መታወቂያን ለሁለታቸሁም አልሰጥም…”አልኩና ስብሰባውን የሚያስተባብረውን አለቃዬን ከውስጥ በስልክ ደውዬ ጠራሁት ፡፡
አለቃዬ ሲሮጥ መጣ ….ዝንጥ ያለ ሱፍ ለብሷ ፤ቦርጭም ስጋም አለው፡፡እኔ ለራሴ ቀጫጫምንም የሌለኝ፡፡
እሱ መምጣቱን ሲያዩ
ወንዱ ጠባቂበአንዴ አከበረኝ አንቺ ምናመን ሲል እንዳልነበርበቃ አሁን እርሶ ይግቡ በኋላ እንነጋገራለንምናምና ማለት ጀመረ ማማን አቃተኝሳኩበት ፤አፈርኩበት፤ቅድም ፍተሻው ላይ የተሳቀኩት ሳያንስ ለሰውዬው አስተሳሰብ እኔ ተሳቀኩኝ
አልገባም አልኩኝአለቃዬኧረ ሰአት እረፍዷል ..እንግዶች እየጠበቁ ነው ምናምንአለ፡፡
አልገባም….መግባት የምፈልገው በራሴ ነው በአንተ ወይም በእገሌ አይደለም፡፡ሀላፊያቸው ይጠራልኝና እሱን አናግሬ እገባለሁከነሱ ጋር በኋላ እነጋገራለሁ አልኩኝ፡፡
ለማንኛሁም ሀላፊው ተጠራ አናገርኩት ገባሁ ስወጣ ግን እነዛ የጥበቃ ሰራተኞችን ዝም ብዬ ላልፋቸው አልፈለኩም ፤ስነምግባሩም አይፈቅድልኝም፡፡ሃላፊያቸው መጣ ፤ይቅርታ ጠየቀኝ፤እነሱም ተጠሩ ይቅርታ ጠየቁ፡፡ይቅርታቸው ግን አልካሰኝም፡፡አላስደሰተኝም፡፡እነዚህ ጥበቃዎች መማር አለባቸው ብዬ አሰብኩኝ፡፡ይቅርታ የእኔ መቤት ስለደረሰብሽ በደል በነሱ ላይ ግን አስተዳደራዊ እርምጃ እንወስዳለንየሀላፊው ንግግር ነበር፡፡አዎ ግዴታችሁ ነውየኔ መልስ ነበር ፡፡
በሳምንቱ
በደርጅታችን በኩል በነዛ ጥበቃዎች ላይ የተወሰደውን አስተዳደራዊ እርምጃ የሚገልጽ ዳብዳቤ ደረሰን፡፡አሁን ተካስኩ አልኩኝ፡፡ትንሽም ቢሆን ከስህተታቸው የተማሩ ይመስለኛል፡፡
እናም እንዲህ ስል አሰብኩኝ፡፡እስከመቼ ይሆን ሰውን በቁመናው፤በአለባበሱ፤በቦርጩ ፤በውፍረቱና መሰል ከሰው ስብዕና ጋር ምንም ተገአቦት በሌላቸው መስፈርቶች መፈረጅና መመዘን የምንተወው?ይሄ ጉዳይስ ከአፓርታይድ በምን ይተናነሳል፡፡ግርም የሚለው ደግሞ የእኛው አፓርታይድ እየደረሰብን ያለው በራሳችን ዜጎች መሆኑ ነው፡፡የሌሎቹስ በነጮቹ ነበር፡፡እኛ ባዶ እጃችንን ሆነን እንዲህ ስንበረበር በሌላ በኩል ደግሞ ምናልባትም ለደህንነት ስጋት የሆኑ ነገሮች የተሸከመ አንድ ፈረንጅ አንድም ጥያቄ ሳይጠየቅ ሰተት ብሎ ይገባል፡፡አይ የኛ ነገር ግራ እኮ ነው ሁሉ ነገራችን፡፡እነሱ ጋር ለደህንነት ከሆነ በቃ ነጭ፤ ጥቁር ፤አርንጓዴ የለም….በቃ ሁልሽም ትበረበሪያለሽ ወይም አትበረበሪም …አለቀ!!
እንደዉም ፈረንጆቹ የራሳችንን ዜጎች እየበረበርን እነሱን ስናሳልፍቸው ምን እያሉ ሙድ እንደሚይዙብን ታውቃላችሁአዳሜ መስሎሽ ነው፤ምን እንደያዝኩ አላረፍሽም …Don’t Judge a book by its cover” hahaha…. የሚሉን አይመስላችሁም፡፡
እናም እባካችሁ
እነሱ እንዲህ ይላሉ “Please don’t judge a book by its cover”…መጽሀፉን በሽፋኑ አትገምግሙት፡፡ጥሩ ነውም መጥፎ ነውም ለማለት መጀመሪያ አንብባችሁ ተረዱትእንደማለት ይሆን፡፡
ቆዳው ስለነጣ ብቻ አትመኑት በአግባቡ ፈትሹት ስለጠቆርንና ስለቀጨጭን ደሞ ጋራዥ እንደገባ መኪና ሞተር መፍታት እስኪቀራችሁ አትበርብሩን ሀሳባችንንም ሳይቀርእባካችሁ ሚዛናዊ ሁኑ፡፡






kuku. A eb እዚሁ ፌስቡክ ላይ በመጻፍ ይታወቃሉ! በሙያቸው ጠበቃ ሲሆኑ የሚያነሷቸውን ማህራዊ ሃሳቦች የሚተቹበት ገጽ አላቸው….እነሆ አድራሻው!  https://www.facebook.com/kuku.eb ኢሜላቸውን ከፈለጉም እነሆ! kuku.eb@facebook.com