Total Pageviews

Wednesday, June 19, 2013

ትዝብት በእንዳለ : እናት ለምን ትሙት ትሂድ አጎንብሳ,,,


 አዲስ አበባ ግንቦት 28፣2005 ዓ ም  :: መንግስት ባወጣው የ 10/ በ90፣20/በ80፣40/በ60 አዲስ ቤት መስሪያ የቁጠባ ደብተር ለማውጣት ከክፍለ ሀገር በመጣው ቀን በበነጋው  ዕለተ ዕሮብ ግንቦት 28፣2005 ነበር:: ቃሊቲ ሚድ ሮክ አከባቢ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ  እኔም እንደዜጋና እንደ አንድ አዲስ አበባ ነዋሪ ቤት መስሪያ የሚሆነኝን ቁጠባ ደብተር ለማውጣት ታላቅ ወንድሜ ከለሊቱ 9:00 ሰዓት ከቤት ወጥቶና 45ኛ ሆኖ በተመዘገበልኝ ተራ ጠብቄ ለመመዝገብ ነበር እዚያ የሄድኩት::  
ታዲያ ባንኩ ከዋናው መንገድ ማለትም ከቃሊቲ ወደ ደብረ ዘይት ከሚወስደው አውራ ጎዳና በስተ ቀኝ ዳር ላይ የሚገኝ ሲሆን :: ከተመዝጋቢው ህዝብ ብዛት የተነሳ ሊመዘገብ ሰልፍ ከያዘ ሰው በተጨማሪ ሰልፍ ሳይዝ የቆመው ሰው አስፋልቱ ጠርዝ ድረስ በቡድን በቡድን እየሆኑ በቤቱ ምዝገባ ላይ የየራሱን ወግ ይዟል ::
አንዱ ቡድን ስለ ህገ ደንቡ እንዲያስረዳ አንዱ የቡድን አባል በጠየቀው ጥያቄ ሁሉም እኔ የገባኝ እንዲህ ነው በሚመስሉ መልኩ ለማስረዳት በመንግስት በተዘጋጀው በራሪ ወረቀት ላይ አንገታቸውን ደፍተዋል:: ከሌላኛው በቡድን ሆነው ከቆሙት መሀከል ደግሞ በዚህ ጉዳይ ብቻ ከስራ ላይ የመጣ የሆነና እዚህ ሶስት ቀናቶችን እንዳሳለፈና ነገር ግን አሁን ወደ ሥራም ለመመለስ እያመነታ መሆኑና ከሁለት ያጣ እንዳይሆን ስጋቱን ለቡድኑ አባላት ያጫውታቻዋል::
 እኔ ለብቻዬ ተነጥዬ ቆሜ ስለነበር በደብ በህዝቡ መሀል ያለውን ነገር መታዘብም ሆነ መመልከት እችል ነበር:: ቢገርማችሁም ባይገርማችሁም ከግማሽ በላይ ህዝብ ጋቢ፣ ሹራብና ካቦርት የለበሰ ነበር ታዲያ ይህ ምን ሊገርመኝ ወንድሜ እኮ 9: 00 ሰዓት ከለሊቱ ወጥቶ እኮ ነው 45ኛ ሆኖ የተመዘገበልኝ :: ይህ ህዝብ ደግሞ ወይ ስምንት ሰዓት ወይ ደግሞ ከዚያ በፊት ሊሆን ይችላል ከቤቱ የወጣው ::  ቤት ፍለጋ ከቤት ውጭ ማደር !
ይህን ትዝብቴን  እንድጭር ያስገደደኝን ዋና ጉዳይ  የሆነውን ዋና እርእሴን አልዘነጋውም። ይሄውላቹ ,,,ወጭ ወራጅ መኪና በዚያ ሲያልፍ ክላክስ ጥሩንባ ያሰማ ነበር :: ምክኒያቱም ጽሁፌን ስጀምር ጠቅሼላቹ ነበር የባንክ ቤቱና አስፋልቱን እርቀት በግምት 16 ሜትር ያህል ነው:: ታዲያ ስም ዝርዝራችንን ሲመዘግቡ መታወቂያችንን ሰብስበው ስለነበር ዕሮብ የተመዘገብነውን ሁሉ ለዓርብ እንድንመለስ ከነገሩን በኋላ መታወቂያችንን ለሶስት ግለሰቦች እንዲመልሱልን ሰጡዋቸው::
የእኔና የሌሎችን መታወቂያ የያዘው ግለ ሰብ መታወቂያችንን ሊመልስልን የሰበሰበን ከአስፋልቱ ጠርዝ ላይ ስለነበር ሰዎች ሲከቡት ሰዉ ከአስፋልቱ ላይ ወጥቶ ነበር:: ኤኬሌ,,, ኤኬሌ,,, ኤኬሌ,,,እያለና ግለሰቡ አቤት ሲል ሰጪው መልኩን ከመታወቂያ ላይ ካለ ፎቶ ጋር እያመሳሰለ ይመልስ ተያይዟል :: ታዲያ አንድ የከባድ መኪና (ሳኒዮ) የጥሩንባ ድምጽ የተሰበሰበውን ህዝብ አስደነበረው :: የመኪናው ጥሩንባ ድምጽ ከፍተኛ ስለነበር ሁሉም ሰው የስድብና የእርግማን ዓይነት ውርጅብኝ ያወርድበት ገባ::   ታዲያ ከዚያ ሁሉ ስድብ፣እርግማንና ከመኪናው ጥሩንባው ጩኧት ይልቅ ጆሮዬ የገባው ድምጽ አንድ አጠገቤ መታወቂያ ሊወስድ የቆመ ወጣት ድምጽ ነበር። አስቀያሚ ስድብ ,,,መቼም የስድብ ጥሩ ባይኖረውም ሹፌሩን አቦ እናትህ እንዲ ላድርግ ብሎ ሲሳደብ ነበር:: እኔ የምገባበት ጠፍቶኝ እንደመሸማቀቅ ብዬ አንገቴን ትከሻዬ ውስጥ ቀብሬ ቀና ስል አንድ እንደ እኔው ስድቡ ልቧን የሰበረባት መልከ መልከም ሴት ጋር ዓይን ለዓይን ተጋጨን :: ይህ ወጣት መጀመሪያ ዓመት የዩንቨርሲቲ የዶርም አባል የሆነውን ልጅ ትዝ እንዲለኝ አስደረገኝ :: ይህ የዶርም አባል የነበረው ልጅ አንድ ቀን FRESH MAN ገና እንደገባን እንዲህ ብሎ ስለሰደበኝ ብቻ ከግቢው በውጤቱ ማነስ (AD) ሆኖ እስከባረር ድረስ አንነጋገርም ነበር::
አቦ በእናታችሁ  ስለእናታችሁ ብላችሁ  እናት የብዙ ነገራችን ምሳሌ ነች እኮ
እ    እ  እ   እ    እ   ናት!
የ ጭንቋ የምጧ የእመሟ ድምጽ ናት::
አዲስ አበባ

ግንቦት 28፣2005 

No comments:

Post a Comment